The Best Construction Tenders Advertiser in Ethiopia

Tenders

Contractor

Read more

 

Consultant

Read more

 

Machinery Rental

Read more

 

Direct Unit Price

Read more

 

የአጥንት ተኝቶ ህክምና ክፍል ግንባታ

Published on:Addis Zemen ( ታኅሣሥ 8፣ 2013 )Place of Bid Competitions:በደ/ብብሕ/ክ/መ በጋሞ ዞን የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል
Rough Estimation of Remaining Time for Bid Submission (don’t use it before check up!)

Please Check the Countdown!

 የመጀመሪያ ዙር ጨረታ ማስታወቂያ

በደ/ብብሕ/ክ/መ በጋሞ ዞን የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በ2013  በጀት ዓመት የአጥንት ተኝቶ ህክምና ክፍል ግንባታ ለማስገንባት በግልጽ ጨረታ ተቋራጮችን አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል::

በዚህ መሠረት፡-

  1. ደረጃቸው BC/GC 6 እና ከዚያ በላይ የሆኑ ተቋራጮች ሆነው የዘመኑን ግብር የከፈሉና ፍቃዳቸውን ያሳደሱ፤ በሥራና ከተማ ልማት ሚ/ር የተመዘገቡና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢዎች ሆነው ኦርጅናል ዶክመንታቸውን ለማመሳከሪያ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  2. አስፈላጊውን የግንባታ ማቴሪያሎችንና መሣሪያዎች በግላቸው አጓጉዘው የሚሠሩና የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  3. የጨረታ ማስከበሪያ Bid Bond /35,000.00 ብር በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ /CPO/ ወይም በጥሬ ወይም ገንዘብ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ ባንክ ጋራንቲ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  4. ተጫራቾች ሕጋዊ ፈቃዳቸውንና ተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ የተመዘገቡበትን ሠርተፍኬት በማቅረብ የጨረታውን ዶክመንት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ እስከ 31 ተከታታይ ቀናት  የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር በመቅረብና በመክፈል የከፈለበትን ወይም ገቢ ያደረጉበትን ደረሰኝ በማቅረብ የጨረታውን ሠነድ መውሰድ ይችላሉ።
  5. ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ በፊት የሥራ ሳይቱን በራሱ ወጪ አይቶ ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።
  6.  የፋይናሽያል ጨረታ ሰነዱ ዋጋ ተሞልቶ አንድ ኦርጅናልና ሁለት ፎቶግራፊክ ኮፒው በተለያየ ፖስታ በሰም ታሽጎ ኦርጅናልና ኮፒ ተብሎ እላዩ ላይ ተጽፎበት፤ በሁሉም ፖስታዎች ላይ ስም፤ አድራሻና የፕሮጀክቱ ስም በመጻፍ ሕጋዊ የሆነ ማህተም በማሳረፍና በመፈረም በሰም በታሸገ አንድ ትልቅ ፖስታ ውስጥ ተከተውና እላይ  የተዘረዘሩ ጽሑፎች እላዩ ላይ በመፃፍ ማህተም በማሳረፍና በመፈረምና  የፋይናንሻል ፖስታዎችን በትልቅ እናት ፖስታ ውስጥ ተከተው እላዩ ላይ በተገለጹ ዝርዝር ጽሑፍ ተጽፎበት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት  32ኛ ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳሬክቶሬት ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  7. የጨረታው ሳጥን የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ቦታ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል ። ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ ሥራ ቀን ላይ በተመሣሣይ ሰዓት ላይ ይከፈታል።
  8. የማንኛውም ተጫራች አርትሜትክ ቼክ ውጤቱ ከተነበበው ዋጋ  አንጻር ከ2% በላይና በታች ሆኖ ከተገኘ ከጨረታው ውጪ ይሆናል። በተመሣሣይ ሪቨት/ቅናሽ ከ10% በላይ በማድረግ ከጨረታው ውጪ  ያደርጋል።
  9. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብት አለው።

በተጨማሪም የተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው አለመገኘት የጨረታውን ሂደት አያስተጓጉልም።

የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል

ተጨማሪ ማብራሪያ

በስልክ ቁጥር 046-881-08-39/09-16-46-74-06 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መን/ በጋሞ ዞን

የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You cannot copy content of this page