The Best Construction Tenders Advertiser in Ethiopia

Tenders

Contractor

Read more

 

Consultant

Read more

 

Machinery Rental

Read more

 

Direct Unit Price

Read more

 

የወረዳ 03 ወጣት ማዕከል እድሳት ስራ

Published on:Addis Zemen ( ጥቅምት 13፣ 2013 )Place of Bid Competitions:Addis Ababa
Remaining Time for Bid Submission (Check it!)

 የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 12/2013

የአራዳ ክፍለ ከተማ ኮንስትራከሽን ፅ/ቤት ለክፍለ ከተማው ሊያስገነባቸው የፈለገውን ስራ የሚሠሩ ስራ ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ለስራው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን፣ የሰው ኃይል በተጨማሪም የሚቀጥሉትን መስፈርቶች በማሟላት የጨረታ ሰነዱን አንድ ብቻ መውስድ ይችላሉ፡፡

ተ.ቁየስራው ዓይነትየሚሰሩበት ወረዳደረጃየጨረታ ሰነድ መሸጥ የሚጀመርበት ቀንየጨረታ ማስገቢያ ቀንየጨረታ መክፈቻ ቀን
1የወረዳ 03 ወጣት ማዕከል እድሳት  ስራወረዳ 3GC 5/BC  5 እና ከዚያ በላይበጋዜጣ  ከወጣበትቀን ጀምሮ በ15ኛው የስራ ቀን 10፡00 ሰዓት በጋዜጣ  ከወጣበትቀን ጀምሮ በ16ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት በጋዜጣ በወጣበት 16ኛው ቀን የስራ ቀን ጠዋት 4፡30 ሰዓት ጀምሮ 
2የወረዳ 08 ወጣት ማዕከል እድሳት ስራወረዳ 8GC 5/BC  5 እና ከዚያ በላይበጋዜጣ  ከወጣበትቀን ጀምሮ በ15ኛው የስራ ቀን 10፡00 ሰዓት በጋዜጣ  ከወጣበትቀን ጀምሮ በ16ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት በጋዜጣ በወጣበት 16ኛው ቀን የስራ ቀን ጠዋት 4፡30 ሰዓት ጀምሮ 
  1. በዘርፉ 2013 የታደሰ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2.  የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ እና የምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ከመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ውንና አንድ ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  4.  ማንኛውም ሥራ ተቋራጭ ሆነ አማካሪ ከመስተዳድሩ ኮንስትራክሽን ቢሮ ተመዝግቦ የብቃት ማረጋገጫ ወይም የአጭር ምዝገባ ሰርተፊኬት ሳይዝ በሴክተሩ መሳተፍ አይችልም፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል  በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ንጻ ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት 3ተኛ ፎቅ ቀርበው በስራ ሰዓት መወሰድ ይችላሉ፡፡
  6. ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው ቀን በእለቱ ባለቤቱና ተወዳዳሪዎች ወይንም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት በጽ/ቤቱ ጠዋት 4፡30 ላይ የሚከፈት ይሆናል፡
  7. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና Bid Bond 70,000.00 ብር ከታወቀ ባንክ በተረጋገጠ የባንክ ዋስትና ወይም ሲፒኦ ለ90 ቀናት የሚያገለግል ሆኖ ከኦሪጅናል ቴክኒካል ጨረታ ሰነዱ ጋር ታሽጎ መቅረብ አለበት፡፡
  8. በተጨማሪነት ስራውን በምን ያህል ጊዜ እንደሚጠናቅቁ የሚገልጽ የስራ መርሃ ግብር /ወርከ ስኬጁል/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነድ አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ፣ ፋይናንሻል ሰነድ አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ በድምሩ ስድስት ሰነድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በተጨማሪም በሰም የታሸገውን 6 ፖስታ በአንድ እናት ፖስታ የድርጅቱንና የተወዳደሩበት ስም በመጻፍ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
  10. ተቋራጮች የስራዎችን የዋጋ ዝርዝር እና የጨረታ ማወዳደሪያ ላይ ስማቸውን ፊርማቸውን አድራሻቸውን ማስፈር ማህተም ማድረግ ኤንቨሎፕን በሰም በማሸግ ማስታወቂያው በወጣበት በ16ኛው ቀን በአራዳ ክ/ከተማ ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እስከ 4፡00 ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡የጨረታው ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለበት መሆን አለበት፡፡ ይህም ከሆነ ተጫራቾች ያስገባው ሰነድ ውድቅ ይሆናል ።
  11. በኮንስትራከሽን ጽ/ቤት በወጡና በሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች ላይ ተቋራጭ ከአንድ በላይ ጨረታ መሳተፍ አይቻልም፡፡
  12. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  13.  ጨረታውን ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማሰታወቂያው በወጣበት በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡ የጨረታው  መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም በበአል ቀን ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡

ለበለጠ መረጃ /ክ/ከ/ኮ/ጽ/ቤት መጠየቅ ይቻላል፡፡

በአራዳ ክፍለ ከተማ ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት

የግዥ ቡድን

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You cannot copy content of this page