The Best Construction Tenders Advertiser in Ethiopia

Tenders

Contractor

Read more

 

Consultant

Read more

 

Machinery Rental

Read more

 

Direct Unit Price

Read more

 

ዶዘር ማሽን፣ ግሬደር እና እስካቫተር እንዲሁም ሎደር ማሽን (Please Check Submission Deadline)

Published on:Addis Zemen ( መስከረም 22፣ 2013 ) /Place of Bid Competitions:ዲላ ከተማ

Remaining Time for Bid Submission

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የዶዘር፣ ግሬደር እና እስካቫተር ማሽን የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 001/2013

የዲላ ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ኮ/ል/ጽ/ቤት በ2013 በጀት ዓመት የማዘጋጃ ቤት ለሚያሰራቸው መሰረተ ልማት ለመንገድ ጥገና እና አዲስ መንገድ ግንባታ የሚያስፈልጉ ማሽኖች ዶዘር ማሽን፣ ግሬደር እና እስካቫተር እንዲሁም ሎደር ማሽን በቀረበው ዝርዝር መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፤

ስለሆነም መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች በኮንስትራክሽን ሥራ የማሽን ኪራይ ዘርፍ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው ሆነው፤ ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፤

  1. የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣
  3. የንግድ ምዝገባ ም/ወረቀት ያላቸው
  4. የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት ያላቸው
  5. የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸው ከሚመለከተው አካል ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  6. የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለእያንዳንዱ ብር 50,000 /ሃምሳ ሺህ ብርበባንክ የተረጋገጠ cpo ማቅረብ የሚችሉ
  8. ማሽነሪ ነዳጅ፣ ቅባት፣ ግሪስ፣ የጥገና ወጭ እና የኦፕሬተር ወጪ እንዲሁም የማመላለሻ ሰርቪስ ጨምሮ መሸፈን የሚችል፡፡
  9. ማሽነሪ በከተማ ውስጥ አሰሪ መ/ቤት ወደሚፈልገው ስፍራ በሎቤድ ማመላለስ የሚችል፡፡
  10. ዘግይቶ የመጣ ፖስታ ተቀባይነት የለውም
  11. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በብር 150 /አንድ መቶ ሃምሳ ብር/ ከፍለው መውሰድ ይችላሉ፡፡
  12.  ተጫራቾች አንድ ኦርጅናልና ፋይናንሻል 2 ኮፒ አንድ ቴክኒካል ኦርጅናልና 2 ኮፒ ሰነዶችን ለየብቻ አሽጎ እናት ፖስታ በአንድ ላይ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ውስጥ በማሸግ ለጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ይህ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ውሰጥ የጨረታ ሰነዱን ከዲላ ከተማ ፋ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት ከቢሮ ቁጥር 6 በመወሰድ መጫረት የምትችሉ፣ መሆኑን እየገለጽን ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ላይ ታሽጎ 430 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በይፋ የሚከፈት መሆኑን እየገለጽን 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፤

*መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-0463310107/3273/3133/ ደውለው ማነጋገር ይችላሉ፡፡

በጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You cannot copy content of this page