| Published on:Be’kur ( ጥቅምት 23፣ 2013 ) | Place of Bid Competitions:በአክብመ የሰሜን ሸዋ ዞን… |
| Submission Date:ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግዥ/ንብ/አስ/ደ/ የስራ ሂደት ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ የጨረታለስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 16 ቀን 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ክፍል 16ኛው ቀን በ4፡30 ይከፈታል፡፡ |
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በሰሜን ሸዋ ዞን በሞጃና ወደራ ወረዳ በሚገኘው የጋውና ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ለ2013 በጀት አመት
- ለተለያዩ የግንባታ አይነቶች የሚውሉ የተለያዩ የግንባታ እቃዎችን፣
- የግንባታ የአጥር ስራ፣ የቢሮ እቃ፣
- የጽዳት፣ የህትመት፣ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣
- የኤሌክትሪክ መለዋወጫ እቃዎች፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣
- የጀኔሬተር ጥገና ፣የሞተር ጥገና ለድጋፍ ሰጭ እና ለባለሙያተኞች የደንብ ልብስ በጋዜጣ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት እና ማሰራት ይፈልጋል፡፡ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር
የምትችሉ ሲሆን፡-
- በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው
- የግዥ መጠን 50000/ሃምሳ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸው የማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትን እናይጠቅመኛል የሚሉትን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- በግንባታ ዘርፍ ለሚወዳደሩ ተወዳዳሪዎች ከደረጃ /6/ በላይ የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የእቃዎችን እና የግንባታ አይነት ዝርዝር መግለጫ /እስፔስፍኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ 50 ብር በመክፈል ግዥ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ከዋና ገንዘብ ያዥ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና/ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ብር ወይም የእቃውን ወይም የግንባታውን ጠቅላላ ዋጋ 1 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመ/ቤቱ መሂ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግዥ/ንብ/አስ/ደ/ የስራ ሂደት ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ የጨረታለስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 16 ቀን 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ክፍል 16ኛው ቀን በ4፡30 ይከፈታል፡፡
- በጥንቃቅን እና አነስተኛ ለተደራጁ ተጫራቾች በመመሪያው መሰረት ድጋፍይደረግላቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱየተጠበቀ ነው፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ 033 89948 60/09 20 86 72 19 ደውለው መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ መዝጊያው ቀን እሁድና ቅዳሜ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን4፡00 ታሽጎ 4፡30 ይከፈታል፡፡
- አድራሻ፡- በአክብመ የሰሜን ሸዋ ዞን ከደ/ብርሃን 100 ኪ.ሜ ወደ ደሴ መስመርከሚወስደው መንገድ ጣርማ በር ዋሻ ወደ ምዕራብ በ40 ኪ.ሜ ገባ ብሎ ነው፡፡
- የጋውና ጤና አጠባበቅ ጣቢያ