Published on:Addis Zemen ( ነሐሴ 28፣ 2012 ) /Place of Bid Competitions:ደሴ ዙሪያ
Remaining Time for Bid Submission
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በአ.ብ.ክ.መ በደቡብ ወሎ ዞን የደሴ ዙሪያ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ለደሴ ዙሪያ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት በአልማ በጀት የጉጉፍቱ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት G+1 አንድ ብሎክ አስር የመማሪያ ክፍል እና ለገታራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት G+0 አንድ ብሎክ አራት የመማሪያ ክፍል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል።
በዚህም መሠረት፡
- የግንባታ የሥራ ፈቃድ ያለው
- ተጫራቾች ለጉጉፍቱ ት/ቤት ደረጃ7 እና ከዚያ በላይ እና ለገታራ ት/ቤት ደረጃ9 እና ከዚያ በላይ ፈቃድ ያላቸው።
- በግንባታ ከ2012 ዓ.ም በፊት የወጣ ፈቃድ ከሆነ የመልካም ሥራ አፈጻጸም መረጃ ማቅረብ የሚገባቸው ሲሆን አዲስ ፈቃድ ያወጡ ከሆነ ግን ማቅረብ አይጠበቅባቸውም።
- የቫት ተመዝጋቢ የሆነ
- የዘመኑን ግብር የከፈለ
- በዘርፉ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለው
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር ማቅረብ የሚችል
- ተጫራቾች ከተራ ቁጥር 1 እስከ 7 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ኦርጅናል ፎቶ ኮፒ በመለየት ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ከወሰዱ በኋላ ዋጋውን ሞልተው ሲያስገቡ ኦርጅናልና ኮፒ በመለየት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- የጨረታውን ሰነድ ከደሴ ዙ/ወ/ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 3 በመምጣት አንድ መቶ ብር (100) በመክፈል መግዛት ይችላሉ::
- ጨረታው ከ29/2/2012 ዓ.ም እስከ 14/1/2013 ዓ.ም ድረስ በአየር ላይ ይውላል።
- ጨረታው በ15/1/2013 ዓ.ም 3፡30 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም 4፡00 ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ለሚሰሩበት ከአቅርቡት ጠቅላላ ዋጋ 2% በጥሬ ገንዘብ፣ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦና ቢድቦንድ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ሰነዶች ላይ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም የተሰረዘ ካለ በፊርማ መረጋገጥ ይኖርበታል::
- ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ደሴ ዙሪያ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት