The Best Construction Tenders Advertiser in Ethiopia

Tenders

Contractor

Read more

 

Consultant

Read more

 

Machinery Rental

Read more

 

Direct Unit Price

Read more

 

የውሃ ቦቴ ፤ ደብል ጋቢና ፒክ አፕና አይሱዙዎችን መከራየት ይፈልጋል፡፡

Published on:Addis Zemen ( ኅዳር 24፣ 2013 )Place of Bid Competitions:በደቡብ መንገዶች ባለስልጣን የጉብሬ ዲስትሪክት
Rough Estimation of Remaining Time for Bid Submission (don’t use it before check up!)

Please Check the Countdown!

ለሶስተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ጉብሬ ዲስትሪክት 004/2013

መ/ቤታችን በደቡብ መንገዶች ባለስልጣን የጉብሬ ዲስትሪክት ጽ/ቤት በሥሩ ላሉት ፕሮጀክቶች እና ጥገና መስመሮች አገልግሎት የሚውሉ የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ማለትም የውሃ ቦቴ ፤ ለሰርቪስ እና ነዳጅ ማመላለሻ አገልግሎት የሚውሉ ደብል ጋቢና ፒክ አፕና አይሱዙዎችን ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም:

  1. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችለውን የዘመኑን ግብር የተከፈለበትን ከሚፈለገው አገልግሎት የተዛመደ የንግድ ሥራ ወይም የአገልግሎት ሥራ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ምስክር ወረቀት እና በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  2. ተጫራቾች ዋጋቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ የፋይናንሻል ፕሮፖዛሉን በተለያየ ፖስታ በማድረግ አንድ ዋና እና አንድ ኮፒ «ኦርጅናል» እና «ኮፒ» በማለት እና የጨረታ ማስከበርያውንም በተለየ ፖስታ ለብቻው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ተጫራቾች ሰነዱን የማይመለስ ብር 50.00 /ሀምሳ ብር /በመክፍል ከዲስትሪክቱ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር መውሰድ ይችላሉ::
  4. የጨረታው አሸናፊ የሚወሰነው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሠረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ክፍት ነው::
  5. አቅራቢዎች ጨረታውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን ገቢ የሚያደርጉበት ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ከቀኑ 600 ሰዓት ድረስ ይሆናል፡፡ ጨረታው በዚያኑ ቀን ከቀኑ 800 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡ ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
  6.  ተጫራቾች የጠቅላላ ዋጋ 1% የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ውጭ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልክ የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም::
  7. ተጫራቾች በጨረታው ደንብና መመሪያ መሠረት ጨረታቸውን ማቅረብ አለባቸው:: ከጨረታው ደንብና መመሪያ ውጭ የሚቀርብ ማንኛውም ጨረታ ተቀባይነት የለውም::

ዲስትሪክቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ::

ስልክ ቁጥር፡- 0113220327 /0113220328 /0118868876

የጉብሬ ዲስትሪክት ጽ/ቤት

አቅ/ን/ አስተዳደር

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You cannot copy content of this page