The Best Construction Tenders Advertiser in Ethiopia

Tenders

Contractor

Read more

 

Consultant

Read more

 

Machinery Rental

Read more

 

Direct Unit Price

Read more

 

…የኮንስትራክሽን መሳሪያዎችን ለመሸጥ ይፈልጋል

Published on:Addis Zemen ( ጥቅምት 3፣ 2013 )Place of Bid Competitions:Addis Ababa
Remaining Time for Bid Submission (check it)

የጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ እና በቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚገኙ ከዚህ በታች የተገለጹትን ያገለገሉ ንብረቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::

ሎት ቁጥርየዕቃው አይነት
ሎት 2የተለያዩ ያገለገሉ አነስተኛ ተሽከርካሪዎች
ሎት 3የተለያዩ ያገለገሉ ከባድ ተሽከርካሪዎችና ተሳቢዎች
ሎት 4የተለያዩ ያገለገሉ የእርሻ እና የኮንስትራክሽን መሳሪያዎች
ሎት 5የተለያዩ ያገለገሉ የተሽከርካሪ፣ የእርሻና የኮንስትራክሽን መሳሪያ ሞተሮች(ኢንጅኖች)ና ኮምፖነንቶች

ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ሁኔታዎች በማሟላት  መወዳደር ይችላሉ::

ሀ) ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት እቃዎቹ በሚገኙበት በኮርፖሬሽኑ ዋና ጽ/ቤት አዲስ አበባ በተሽከርካሪዎች አስተዳደርና ጥገና ዘርፍ እና በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማለትም ሞጆ፣ (ሀዋሳ (ሻሎ)፣ አሰላ ጎንዴ፣ ባህርዳር (ቁንዝላ)፣ ቻግኒ፣ አርዳይታ በመቅረብ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 150.00(አንድ መቶ ሃምሳ ብር ) በመክፈል በተራ ፊደል ለከተገለፁት ቦታ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ::

ለ) የጨረታ ሰነድ ሽያጭ የሚካሔደው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በዘርፉ ጽ/ቤት እና (በሀዋሳ፣ በአሰላ፣ በባህርዳር፣ በቻግኒ፣ በአርዳይታ እና ሞጆ) ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት ክፍት ይሆናል:: ጨረታውም 10ኛው የሥራ ቀን ከቀኑ 1000 ሰዓት ተዘግቶ የቅ/ጽ/ቤት ሰነዶች ተሰብስበው ከመጡ በኋላ

13ኛው የሥራ ቀን፡

  • ሎት 2 ከቀኑ 4፡00 ሰዓት
  • ሎት 3 ከቀኑ 6፡00 ሰዓት
  • ሎት 4 እና 5 ከቀኑ 8፡00 ሰዓት

ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ጽ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ አዲስ አበባ ይከፈታል::

ሐ) ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለእያንዳንዱ ሎት ማለትም፡

  • ሎት 2፡- ለአነስተኛ ተሽከርካሪዎች ለእያንዳንዱ ለሚወዳደሩበት ተሽከርካሪ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር)
  • ሎት 3፡- ለከባድ ተሽከርካሪዎችና ተሳቢዎች ለእያንዳንዱ ለሚወዳደሩበት ተሽከርካሪ ዋጋ ብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር)
  • ሎት 4፡- ለእርሻ እና ኮንስትራክሽን መሳሪያዎች ለእያንዳንዱ ለሚወዳደሩበት መሳሪያ ብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር)
  • ሎት 5፡- ለተለያዩ የተሽከርካሪ፣የእርሻና የኮንስትራክሽን መሳሪያ ሞተሮች (ኢንጅኖች) እና ኮምፖነንቶች ለእያንዳንዱ ለሚወዳደሩበት፡
    • ሎት 5.1 የተለያዩ ኮምፖነንቶች የመግዥያ ዋጋውን ብር 2% እና
    • ሎት 5.2 ለየተለያዩ ሞተሮች ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ (CPO) በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (የተሸከርካሪዎች አስተዳደርና ጥገና ዘርፍ) ስም በማዘጋጀት ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::

መ) ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ዕቃ የሚገዙበትን ዋጋ ከተጨማሪ ዕሴት ታክስ በፊት በተዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ሠንጠረዥ ላይ በዝርዝር በማመላከት ማቅረብ አለባቸው::

ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

አድራሻ፡- የቃሊቲ ጉምሩክ ፊት ለፊት የቃሊቲ ባቡር የመጨረሻ ጣቢያ አዋሽ ባንክ ያለበት ህንፃ በስተጀርባ የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ህንፃ ያለበት ግቢ የተሽከርካሪዎች አስተዳደርና ጥገና ዘርፍ ቢሮ ቁጥር 312

ስልክ ቁጥር 0114-43-20-18፣ 011-470-84-70/ 0114-42-5637

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You cannot copy content of this page