Published on:Be’kur ( ጳጉሜ 2፣ 2012 ) /Place of Bid Competitions:አማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰከላ ወረዳ
Remaining Time for Bid Submission
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕ/ጐጃም ዞን ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብ/ መምሪያ የሰከላ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ለሰከላ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ከአልማ በተገኘ የበጀት ድጋፍ አማካኝነት
- ሎት1 የከበሳ ሃይስኩል የቢሮ አስተዳዳር ግንባታ ለማስጨረስ
- ሎት2 የአባግስ ሃይስኩል የቢሮ አስተዳዳር ግንባታ ለማስጨረስ
- ሎት3 የአምቢሲ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የመማሪያ ክላስ ግንባታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማስገንባት ይፈልጋል ፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፣
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፣
- ተጫራቾች ደረጃ 9 እና በላይ መሆን አለባቸዉ
- የግዥው መጠን ከብር 200 ሺህ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-5 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገነቡ የሰራ ዝርዝሮችን መግለጫ /ስፔስፊኬሽን /ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 50/አምሳ ብር ብቻ / በመክፈል ከግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ክፍል ከጳጉሜ 02/2012 እስከ መስከረም 17/2013 ዓ/ም 11፡30 ድረስ ብቻ ቢሮ ቁጥር 04 መግዛት ይችላሉ
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም ቢድ ቦንድ ለሚወዳደሩበት(የሞሉትን) ዋጋ 1.5 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ እና በኢ/ዝ የተደራጁ ከሆነ በጨረታ በወጣበት ጊዜ ዉስጥ የተጻፈ የድጋፍ ደብዳቤ ማስያዝ አለባቸው ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሣቡን በአንድ ወይም በአንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በሰከላ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት በግዥና ንብረት አስተዳድር ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 04 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ መስከረም 18/ 2013 ዓ/ም 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ክፍል በቢሮ ቁጥር 04 መስከረም 18/ 2013 ዓ/ም በ4፡10 ይከፈታል
- አሸናፊ የሚለየዉ በጠቅላላ ድምር ዝቅተኛ ዋጋ ሆኖ የስራ ዝራዝሩን አስተካክሎ መሙላትና የሁሉንም የነጠላ ዋጋ ያልሞላ በጫራታዉ ወድቅ ይሆናል፡፡
- አሸናፊ በተገለጸ ከአምስት(5) ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ ባሉት አምስት(5) ተከታታይ ቀናት ዉስጥ ያሸነፉበትን የጨረታ ማስከበሪያ 10 በመቶ በሰከላ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ስም በባንክ በተረጋገጠ ስፒኦ በማሲያዝ ዉል መዉሰድ አለባቸዉ በተባለዉ ቀን የማይመጣ ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ የምንወረስ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- መ/ቤቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡
- በጨረታ ማስታወቂያዉ ያልተካተተ በግዥ መመሪያ የምንገዛ ይሆናል
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 04 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በፋክስ ቁጥር 0582590442 በመላክ ወይም በስልክ 0582590009/6 በመደወል ማግኘት ይችላሉ ፡፡
የሰከላ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት