| Published on:Addis Zemen ( ታኅሣሥ 14፣ 2013 ) | Place of Bid Competitions:ሐዋሳ |
| Rough Estimation of Remaining Time for Bid Submission (don’t use it before check up!) |
Please Check the Countdown!
የሶላር ፋውንዴሽን እና አጥር ሥራ ጨረታ ማስታወቂያ
ኢትዮ ቴሌኮም የደቡብ ሪጅን ጽ/ቤት ለሚገኘው የሶላር ፋውንዴሽን እና አጥር ሥራ በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በዘርፉ የስራ ፈቃድ ያላችሁና ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ድርጅቶች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ከሐዋሳ ዋናው ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 307 በመቅረብ የማይመለስ 100 ብር ከፍለው ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
| ተ.ቁ | የሳይት ቦታ | የጨረታ መለያ | ጨረታው የሚቆይበት ጊዜ | የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት | የጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓት | የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር |
| 1 | ኤልጎፍ | 4047340 | ለ 15 ቀን | ታህሳስ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት | ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት | 20,000.00 |
| 2 | ጉጂ ዳዋ | 4047341 | ለ 15 ቀን | ታህሳስ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት | ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት | 20,000.00 |
| 3 | ዋደራ | 4047342 | ለ 15 ቀን | ታህሳስ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት | ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት | 20,000.00 |
| 4 | አሮሬሳ | 4047343 | ለ 15 ቀን | ታህሳስ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት | ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት | 20,000.00 |
- የጨረታ ማስከበሪያ 20,000 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማቅረብ የሚችል
- የ2013 ዓ.ም ግብር የከፈለ እና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው
- የቫት እና የቲን ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል
- በደረጃ አምስት (5) እና ከዚያ በላይ የስራ ልምድ ያለው ሆኖ በዘርፉ አንድ የመልካም ሥራ አፈፃፀም የክፍያ ሰርተፍኬት እና ውል በተመሳሳይ ማቅረብ የሚችል
- ከዚህ በፊት ከድርጅታችን ጋር ሥራ ሰርተው በወቅቱ ያላስረከቡና ከድርጅታችን ጋር ውል ገብተው በሥራ ላይ ያሉ ኮንትራክተሮች በዚህ ጨረታ መወዳደር አይችሉም፡፡
- በገቢዎች አስተዳደር ባለስልጣን በጨረታ ላይ መሳተፍ የሚያስችል ደብዳቤ ያለው እና ደብዳቤውን ማቅረብ የሚችል
- ተጫራቾች ፡- ፋይናንሻል ዋናው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ቴክኒካል ዶኩመንት ዋናው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ፋይናንሻል ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ (ሁለት ኮፒ ) ቴክኒካል ዶክመንት ኮፒውን (ሁለት ኮፒ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እንዲሁም ሲፒኦ ለየብቻ አድርገው በአንድ እናት ፖስታ በማድረግ ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ
መስሪያ ቤቱ በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም