| Published on:Addis Zemen ( ጥቅምት 10፣ 2013 ) | Place of Bid Competitions:ጋምቤላ |
Remaining Time for Bid Submission (Check it!)
ለመንገድ ግንባታ የሚውሉ ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎች ኪራይ
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 001/2013
የጋምቤላ ክልል ገጠር መንገዶች ባለስልጣን የተለያዩ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች፣ ገልባጭ መኪናዎችና ቀላል ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል፡፡
| ተ.ቁ | የተሽከርካሪው /የማሽነሪው አይነት | ብዛት |
| 1 | ሞተር ግሬደር 180 የፈረስ ጉልበት እና ከዚያ በላይ ጉልበት ያለው | 3 |
| 2 | ዶዘር 300 የፈረስ ጉልበት እና ከዚያ በላይ ጉልበት ያለው | 2 |
| 3 | ሮለር 14 ቶን ክብደት እና ከዚያ በላይ ክብደት ያለው | 3 |
| 4 | ሎደር 3 ሜትር ኪዩብ የሚጭን እና ከዚያ በላይ የሚጭን | 2 |
| 5 | ቼን ኤክስካቫተር 200 የፈረስ ጉልበት እና ከዚያ በላይ | 1 |
| 6 | የውሃ ቦቴ 13,000 ሊትር እና ከዚያ በላይ መጫን የሚችል | 3 |
| 7 | ገልባጭ መኪና 14 ሜትር ኪዩብ የሚጭን እና ከዚያ በላይ የሚጭን | 15 |
| 8 | ሰርቪስ መኪና ሎንግ ቤዝ ሾፌሩን ጨምሮ 10 ሰው መጫን የሚችል | 4 |
| 9 | ሰርቪስ መኪና ፒክ አፕ ደብል ገቢና ሾፌሩን ጨምሮ 5 ሰው መጫን የሚችል | 2 |
| 10 | ሰርቪስ መኪና ሲንግል ካፕ ገቢና ሾፌሩን ጨምሮ 2 ሰው መጫን የሚችል | 3 |
በዝርዝር ከላይ የተመለከቱትን ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ሙሉ በሙሉ ለማከራየት የምትፈልጉ ተጫራቾች በጋምቤላ ገጠር መንገዶች ባለስልጣን የግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 6 በመገኘት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል የጨረታ ሠነዱን ዘውትር በስራ ሰዓት በመግዛት ረቡዕ 2/3/2013 ዓ.ም ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ በዚሁ ቀንም ጨረታው ሁሉም ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጋምቤላ ገጠር መንገዶች ባለሥልጣን የግዢና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 6 ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተከፍቶ 4፡30 ሰዓት ድረስ የጨረታውን ሰነድ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ካስገቡ በኋላ በዕለቱ ጨረታው ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የዘመኑ ግብር የከፈሉበት፣ ከሚፈለገው አገልግሎት ጋር ተዛማች የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ወይም የአገልግሎት ሥራ ፈቃድ፣ የአገር ውስጥ ገቢ የድጋፍ ደብዳቤ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት እና የዕቃ አቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የሚወሰነው በጨረታ ሰነድ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሰረት ብቻ ሲሆን ጨረታው ለማንኛውም ብሔራዊ አቅራቢ ድርጅት ክፍት ነው፡፡ የጨረታ ሰነዱ የተዘጋጀው በአማርኛ ቋንቋ ነው፡፡
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ዓይነት የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎች ጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪ በባንክ በተረጋገጠ CPO ለብቻው በማሸግ ወይም በጥሬ ገንዘብ ገቢ የተደረገበት ሞዴል / አብሮ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልክ የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዕለቱ ረቡዕ 2/3/2013 ዓ.ም ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን የሚያስገቡበት የመጨረሻ ዕለት ሲሆን በዕለቱ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ይከፈት እና 4፡30 ሰዓት ይዘጋል፡፡ የጨረታው የመክፈቻው ቀን በሰንበት ወይም በበዓላት ቀን ላይ ከዋለ በማግስቱ በስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ጨረታው ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ደንብና መመሪያው መሠረት ሙሉ የጨረታ ሰነዳቸውን ማቅረብ አለባቸው፡፡ ከጨረታው ደንብና መመሪያ ውጭ የሚቀርብ ማንኛውም የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
የጋምቤላ ገጠር መንገዶች ባለስልጣን
የስልክ ቁጥር 047-551-0835/047-551-1175/047-551-2376
ጋምቤላ
የጋምቤላ ክልል ገጠር መንገዶች ባለስልጣን