The Best Construction Tenders Advertiser in Ethiopia

Tenders

Contractor

Read more

 

Consultant

Read more

 

Machinery Rental

Read more

 

Direct Unit Price

Read more

 

አንድ ብሎክ ባለ አራት ክፍል ትምህርት ቤት

Published on:Be’kur ( ታኅሣሥ 19፣ 2013 )Place of Bid Competitions:በአማራ ክልል በሰሜን ጐንደር የዳባት ወረዳ
Rough Estimation of Remaining Time for Bid Submission (don’t use it before check up!)

Please Check the Countdown!

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

በአማራ ክልል በሰሜን ጐንደር የዳባት ወረዳ ገንዘብ ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት በ2013 ዓ.ም በአልማ በጀት በጭላ ቀበሌ አንድ ብሎክ ባለ አራት ክፍል ትምህርት ቤት በሙሉ ዋጋ ለማስገንባት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈለጋል:: ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ያሟላችሁ ተጫራቾች በውድድሩ እንድትሳተፉ እያሳሰብን ተጫራቾች ፡-

  1. ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያለው፣
  2. የዘመኑን ግብር አጠቃሎ በመክፈል ንግድ ፍቃዱን ያደሰ፣
  3. የቫት ተመዝጋቢ የሆነና የግብር ከፋይ ቁጥር /ቲን/ ያለው/ያላት፣
  4. የግንባታ ፈቃዱ ደረጃ 8 እና ከዛ በላይ፣
  5. ተጫራቾች በተራ ቁጥር 1-4 የተመለከቱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ ከማጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፣
  6. ተጫራቾች የግንባታውን ሙሉ ስፔስፊኬሽን ወይም ዝርዝሩን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፣
  7. መ/ቤቱ 20 በመቶ ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል፣
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 50 የኢትዮጵያ በእያንዳንዱ ሎት በመክፈል ዳባት ወረዳ ግ/ፋ/ን/አስ/ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 በተከታታይ ቀናት ማግኘት ይችላሉ፣
  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት ብር ዋጋ የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ 1 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማለትም ግዥና ፋይናንስ ካርኒ በመቁረጥ ኮፒ በማድረግ በጨረታ ፖስታ ላይ በማሸግ ማስያዝ አለባቸው፣
  10. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ዋናና ቅጅ በመለየት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ሆኖ ለየብቻቸው ተለይተው ዳ/ወ/ግ/ፋ/ን/አስ/ደጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ቀናት ከታህሳስ 19/2013 ዓ.ም እስከ ጥር 3/2013 ዓ.ም ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
  11. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ፋ/ን/አስ/ቢሮ ቁጥር 23 በቀን 4/5/2013 ዓ.ም ከጥዋቱ 4፡00 ታሽጐ በ4፡30 ይከፈታል፣
  12.  መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
  13. ተጫራቾች ስለ ጨረታው ተጨማሪ ዝርዝር ማብራሪያ ከፈለጉ ዳባት ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 23 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 113 0410 ወይም 058 113 0205 በመደወል ማግኘት እንደሚቻል እናሳውቃለን::

ማሳሰቢያ ፡- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ብሔራዊ በአል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይሆናል::

የዳ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You cannot copy content of this page