The Best Construction Tenders Advertiser in Ethiopia

Tenders

Contractor

Read more

 

Consultant

Read more

 

Machinery Rental

Read more

 

Direct Unit Price

Read more

 

የመጸዳጃ ቤት ግንባታ

Published on:Addis Zemen ( ኅዳር 29፣ 2013 )Place of Bid Competitions:ከአዲስ አበባ 130 ኪ.ሜ ርቀት ወደ ደብረብርሃን 80 ኪ.ሜ ርቀት
Rough Estimation of Remaining Time for Bid Submission (don’t use it before check up!)

Please Check the Countdown!

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 02/13

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን የሀ/ማ/ከ/ወ ገ/ኢ/ት/ ፅ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ ሴ/መ/ቤቶች ለ2013 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ፤

  1. የጽህፈት መሳሪያዎች ለሁለተኛ ጊዜ
  2. ቋሚ አላቂ እቃ ለሁለተኛ ጊዜ
  3. ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ለሁለተኛ ጊዜ
  4. የተዘጋጁ ደንብ ልብስ ፣ብትን ጨርቅ፣ ጫማዎችና ልብስ ስፌት ለሁለተኛ ጊዜ
  5. ፈርኒቸር ለመጀመሪያ ጊዜ
  6. የእንስሳት መድሀኒት ለሁለተኛ ጊዜ
  7. የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ለመጀመሪያ ጊዜ

ስለዚህ:

  1. በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው እና የታደሰ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት የአቅራቢነት ማስረጃ ያላቸው
  3. የግዥው መጠን ብር 200000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክርነት ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው
  5. የሚገዙ እቃዎችን አይነት ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊክሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ::
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 50/ሀምሳ ብር/ብቻ በመክፈል ከግዥ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 8 ማግኘት ይችላሉ
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይችላሉ፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በሀ/ማ/ከ/ወ/ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ግዥ ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 8 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 330 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግዥ የን/ አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 8 በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ይከፈታል፡፡ 16ኛው ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
  10. ተጫራቹ ናሙና ለሚያስፈልጋቸው እቃዎች ጨረታው ከመዘጋቱ ከሁለት ቀን በፊት ናሙና ማቅረብ መቻል አለበት፡፡
  11. መ/ቤቱ ጨረታውን እንዳዋጭነቱ በተናጠል ወይም በጥቅል ሊሰጥ ይችላል፡፡
  12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 8 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0116190146/148 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

አድራሻ ፣ከአዲስ አበባ 130 ኪ.ሜ ርቀት ወደ ደብረብርሃን 80 ኪ.ሜ ርቀት በሚወስደው አስፋልት ከሸኖ ከተማ አለፍ ብሎ ወደ ምስራቅ 39 ኪ.ሜ ገባ ብሎ እንገኛለን፡

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን የሀገረማርያም ከሰም ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት

ሾላ -ገበያ

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You cannot copy content of this page