| Published on:Addis Zemen ( ኅዳር 17፣ 2013 ) | Place of Bid Competitions:Addis Ababa |
| Rough Estimation of Remaining Time for Bid Submission (don’t use it before check up!) |
Please Check the Countdown!
ብሔራዊ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 01/2013
የብሔራዊ የደም’ባንክ አገልግሎት ለ2013 ዓም በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ እቃ፤ አገልግሎቶች እና ግንባታ ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሰረት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾችን እንጋብዛለን፡፡
| ተ.ቁ | ሎት | ዝርዝር ሎት ዓይነት | የጨረታሰነድዋጋ | የጨረታ ማስከበሪያመጠን |
| 1 | ሎት 1 | የደንብ ልብስ፣ ፍራሽ እና የአልጋ ልብስ | 100.00 | 15,000.00 |
| 2 | ሎት2 | ህትመት | 100.00 | 75,000.00 |
| 3 | ሎት3 | የህክምና መገልገያዎችና መሳሪያዎች(አላቂ እናቋሚ) | 100.00 | 100,000.00 |
| 4 | ሎት4 | ምግብ (ለስላሳ፣ ውሃ እና ብስኩት) | 100.00 | 30,000.00 |
| 5 | ሎት5 | የጽዳት ዕቃዎች | 100.00 | 10,000.00 |
| 6 | ሎት6 | የመኪና መለዋወጫ፣ ባትሪ እና ጎማ | 100.00 | 50,000.00 |
| 7 | ሎት7 | የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች | 100.00 | 40,000.00 |
| 8 | ሎት8 | የባዮ-ሜዲካል ወርክሾፕ መሳሪያናመለዋወጫዎች | 100.00 | 50,000.00 |
| 9 | ሎት9 | የህንጻ ቁሳቁስና ተገጣጣሚዎች | 100.00 | 10,000.00 |
| 10 | ሎት10 | የጽዳትና የጥበቃ አገልግሎት | 100.00 | 10,000.00 |
| 11 | ሎት11 | የኤንሲነሬተር አገልግሎት | 100.00 | 10,000.00 |
| 12 | ሎት12 | የድንኳን ኪራይ አገልግሎት | 100.00 | 10,000.00 |
| 13 | ሎት13 | መሰረተ ልማት እድሳትና ጥገና | 100.00 | 20,000.00 |
- ተጫራቶች በዘርፉ የተሰማሩና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ኖሯቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN No) ያላቸውና የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00/ አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 20 ተከታታይ የስራ ቀናት በአገልግሎቱ ግዥና ፋይናንስ mአቅርቦት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 303 ቀርበው መግዛት ይችላሉ፤
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ጨረታው በአየር ላይ ከዋለ ጀምሮ እስከ 21 ኛው ተከታታይ የስራ ቀን 4:00 ሰዓት ድረስ መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን የጨረታ ሳጥኑ በእለቱ ከጠዋቱ 4.00 ሰዓት ተዘግቶ ከጠዋቱ 4.30 ይከፈታል፡፡ 21 ኛው ቀን የእረፍት ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቹ የጨረታውን ኦሪጅናልና ቅጂ፣ አማራጭ ጨረታዎችን ጨምሮ በተጫራቾች መመሪያ አንቀጽ 20 መሠረት በተለያዩ ኤንቨሎፖች ውስጥ “ኦሪጅናል” እና “ቅጂ” በሚል ምልክት በማድረግ ማሸግ የሚኖርባቸው ሲሆን እነዚህ ኦሪጂናልና ቅጂዎችን የያዙ ኤንቨሎፖች በሌላ ትልቅ ኤንቨሎፕ ውስጥ በአንድ ላይ ተከተው ማሸግ እና በጉልህ የተወዳደሩበትን ሎት ቁጥር መፃፍ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ሎት ከላይ በሰንጠረዡ፣ በተገለጸው መሰረት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከጨረታው ሰነድ ጋር በማሸግ ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ አቅራቢዎች ከአደራጃቸው መ/ቤት አንድ ወር ያልበለጠ ጊዜ የሆነ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በኤጀንሲው የአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ ስለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- . ተጫራቾች ዋጋሲሞሉ ከቫት በፊትና በኋላ መሆኑን በግልጽ ማመልከት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራጮች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ በግልጽ ያልተለዩ እና አጠራጣሪ የሆኑ እቃዎችና አገልግሎቶች ቢያጋጥማቸው የራሳቸውን አማራጭ የፍላጎት መግለጫ /specifications/ ማያያዝ እና ለሁሉም እቃዎች በጨረታው እለት ናሙና ማቅረብ ግዴታ ነው፡፡ ሆኖም መ/ቤቱ በ2009 ዓ.ም ፤ በ2010 ዓ.ም እና በ2011 ዓ.ም. ባወጣው ግልጽ ጨረታ ላይ አሸንፈው በውላቸው መሰረት በከፊል/በሙሉ ያልፈጸሙ የጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅቶችንና ሌሎች አቅራቢዎች በጨረታው አይሳተፉም፡፡
- ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለጸላቸው ጊዜ ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ጨረታ ላይ ማሳተፊያ ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ ከተከፈተ በኋላ የሚቀርብ የመወዳደሪያ ፖስታ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
- መ/ቤቱ በግዥ መመሪያው መሰረት ከሚገዛው እቃ 20% ሊቀንስ ወይም ሊጨምር ይችላል፡፡
- አገልግሎቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ዘወትር በስራ ሰዓት በስልክ ቁጥር 0922596333/0933225921 በመደወል መረዳት ይቻላል፡፡
• አድራሻ፡- ብሔራዊ የደም ባንክ አገልግሎት ልደታ ክ/ከተማ ጎማ ቁጠባ ጤና ሚኒስቴር አጠገብ ይገኛል፡፡
ብሔራዊ የደም ባንክ አገልግሎት