| Published on:Addis Zemen ( ኅዳር 13፣ 2013 ) | Place of Bid Competitions:በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ወሎ ዞን የሀብሩ ወረዳ |
| Rough Estimation of Remaining Time for Bid Submission (don’t use it before check up!) |
Please Check the Countdown!
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 02 /2013
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ወሎ ዞን የሀብሩ ወረዳ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት ለሀብሩ ወረዳ ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽ/ቤት በሬድ ፕላስ በጀት የችግኝ ማፍያ ፕላስቲክ ፖሊቲንቲዩብ/፡ በሀብሩ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት በዋን ዋሽ በጀት
- የመርኮታ ጤና ኬላ መጸዳጃ ቤት ግንባታ ከደረጃ 9 በላይ BC እና GC ተቋራጮች በሙሉ ዋጋና በሀብሩ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የአሊመንታ ት/ቤት ግንባታ ከደረጃ 9 በላይ BC እና Gር ተቋራጮች
- በሙሉ ዋጋ የሀብሩ ወረዳ ውሃ ማእድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት የውሀ ግንባታ ስራ ለኦርቲዥ ያኖችና ደረጃ 9 እና ከዚያ በላይ WC ስራ ፍቃድ ባላቸው የእጅ ዋጋ እና
- የውሃ ግንባታ አገልግሎት የሚውል የውሃ እቃ ማቴሪያል ግዥ በዘርፉ በተሰማሩበት የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸውን ኣቅራቢዎችና ባለሙያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለማሰራት ይፈልጋል ፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡
- የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው በተጠየቁት የግዥ አይነትና ዘርፍ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ::
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር TIN/ ያላቸው፡፡
- የግዥ መጠኑ ከብር 200000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በውሉ መሰረት ያሸነፈበትን እቃ ግዥ ኦርጅናል እቃዎች ማቅረብ የሚችል፡፡
- ማስታውቂያው በኣየር ላይ የሚቆይበት ጊዜ ለስሬድ ፕላስ ስጀት የፖሊቲን ቲዩብ እና በመደበኛ ካፒታል በጀት የውሃ እቃ ግዥ ጨረታ በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀን እስከ11፡30 ለአልማ በጀት ኣሊመንታ ት/ቤት ግንባታና ለውሃ ግንባታ ማስታወቂያው በኣየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 ቀን እና እስከ 11፡30 በዋን ዋሽ በጀት የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ማስታወቂያው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 30 ቀናት እስከ 11፡30 የስራ ቀን ድረስ ብቻ ነው፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ 1 % በCPO ያስይዛሉ ወይም ገንዘቡን አስቀድሞ ገቢ በማድረግ ገቢያደረጉበትን ደረሰኝ ኮፒ ፖስታ ውስጥ በማድረግ ያቀርባሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድና መመሪያ ለእያንዳንዱ ለተጠየቀ ግዥ ሰነድ በማይመለስ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን ዝርዝር ከሰኞ እስከ አርብ በስራ ሰአት ጨረታው አየር ላይ ከሚቆይበት መጨረሻ ቀን እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ ቢሮ ቁጥር 12 በመገኘት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ኦርጅናል እና ኮፒ በማለት ለሬድ ፕላስ በጀት የፖሊቲን ቲዩብ ግዥ በ16ኛው ቀን እና ለአልማ ግንባታ በ 21ኛው ቀን እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዋን ዋሽ ግንባታ በ31ኛው ቀን እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ ቢሮ ቁጥር 12 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡
- ጨረታው ለዋን ዋሽ በጀት የመጸዳጃ ቤት ግንባታ በ32ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ሰዓት ይከፈታል ፡ በሬድ ፕላስ በጀት የፖሊቲን ቱዩብና የውሃ እቃ ግዥ በ17ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ሰዓት ይከፈታል ለአልማ በጀት ግንባታ የአሊመንታ ት/ቤት ግንባታና መደበኛ በጀት የውሃ ግንባታ በ22ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች እራሳቸው ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 12 ይከፈታል፡፡ተጫራቾች ባይገኙም ፖስታውን ከፍተን የምናወዳድር መሆኑን ይታወቅ::
- ጨረታው የሚከፈትበት ዕለት የስራ ቀን ካልሆነ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥልው የስራ ቀን ከላይ በተገለጸው በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ የሚከፈት ይሆናል::
- ተጫራች በጨረታ ሰነዱ ላይ ሙሉ አድራሻ ፣ ማህተም ፊርማ እና ሌሎች መረጃዎችን ኣሟልተው ማቅረብ አለባቸው::
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
- በጨረታው አሸናፊ ከሆነ 10% የውል ማስከበሪያ CPO ወይም በባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርቦታል፡፡
- በጨረታው ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0333330585 በመደወል ወይም በአካል በመቅረብ መጠየቅ ይችላሉ።
የሀብሩ ወረዳ ገ/ኢ/ት ጽ/ቤት