| Published on:Addis Zemen ( ጥቅምት 5፣ 2013 ) | Place of Bid Competitions:Addis Ababa |
Remaining Time for Bid Submission
የሎቤድ /ሃይቤድ/ ተሽከርካሪዎች የትራንስፖርት
ኪራይ አቅርቦት የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሎቤድ ሃይቤድ/ የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ከባድ ተሸከርካሪዎችን በተቀመጠው ቁርጥ ዋጋ መሰረት ፍላጎቱ ሲኖር ተከራይቶ በሃገሪቱ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ለሚገኙ የመንገድ፣ የውሃ እና የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶችና የተለያዩ የኮንስትራክሽን ግብዓቶችና ማሽነሪዎችን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሠረት እንደየመንገዱ ዓይነትና ባህሪ እና የመሬት አቀማመጥ ተጨባጭ ሁኔታተጠንቶ በተዘጋጀው የኪራይ ዋጋ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የምትፈልጉ አከራዮችእና ትራንስፖርተሮች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት አንስቶ ባሉትአስራ አምስት /15/ ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎችኮርፖሬሽን ቃሊቲ በሚገኘው ኮንስት/ መሣሪ/ማሽነ/ማኔጅ/ዘርፍ የማሽነሪ ኪራይ ክፍል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን በምዝገባው ለመሳተፍ የሚከተሉትንመስፈርቶች ማሟላት የሚኖርባቸው መሆኑን እንገለፃለን፡፡
- አከራዮች ትራንስፖርተሮች በምዝገባው ለመሳተፍ የሚችሉት በግል ንብረታቸው ወይምህጋዊ ውክልና ማቅረብ በሚችሉባቸው ተሽከርካሪዎች ብቻ ነው፡፡
- አከራዮች /ትራንስፖርተሮች በኮርፖሬሽኑ ስር ለሚተዳደሩ ፕሮጀክቶች ለመሰማራትፍላጎት ያላቸው ብቻ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡
- አከራዮች ትራንስፖርተሮች ለምዝገባው የሚያቀርቧቸው ተሽከርካሪዎች በጥሩ ይዞታ |ያሉ መሆን አለባቸው፡፡
- አከራዮች/ትራንስፖርተሮች በአቅራቢዎች ዝርዝር ስለመመዝገባቸው የሚያስረዳ ሠርተፊኬት ለምዝገባ ሲቀርቡ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- በምዝገባው ለመካፈል የሚፈልጉ አከራዮች/ ትራንስፖርተሮች በተራ ቁጥር 5 ከተጠቀሰው በተጨማሪ የዘመኑን ግብር የተከፈለበትንና ከሚፈለገው አገልግሎት ጋር የተዛመደበ2012 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ በምዝገባው ለመሳተፍ ከገቢዎች ባለሥልጣን የተሰጠየድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አከራዮች/ ትራንስፖርተሮች የሚያቀርቧቸው ተሽከርካሪዎች የመድን ዋስትና የተገባላቸውመሆን አለባቸው፡፡
የአከራዮች/ትራንስፖርተሮች ምዝገባ አካሄድ፡
- ምዝገባ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ቃሊቲ በሚገኘው ኮንስት/መሣሪ/ማሽነ/ማኔጅ/ዘርፍ የኪራይ መሳሪያ አስተዳደር ቡድን ቡድንነው፡፡
- የተሽከርካሪዎች የመጫን አቅም ከተሽከርካሪው አምራች ድርጅት የተሰጠ ማረጋገጫተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- አከራዮች ትራንስፖርተሮች ይህ ማስታወቂያ ክፍት ሆኖ በሚቆይበት ጊዜ ለምዝገባየሚያስፈልገውን መረጃ በመያዝ በአካል ቀርበው መመዝገብ ይኖርባቸዋል፡
- የአከራዮች የትራንስፖርተሮች ምዝገባ የሚካሄደው በተሽከርካሪው የመጫን አቅምናአከራዩ የስምሪት ፍላጎት ፕሮጀክቱ ተለይቶ ይሆናል፡፡
- አከራዮች በጊዜ ገደቡ ውስጥ ለመመዝገባቸው በምዝገባ ሰነዱ ላይ በስማቸውአንፃር መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡
| ተ.ቁ | የፕሮጀክቱ ስም | ከአዲስ አበባ ያለው ርቀት | |
| አስፋልት | ጠጠር | ||
| 1 | ቃሊቲ ዕቃ ግ/ቤት | ||
| 2 | የአላባ- አንጋጫ-ዋቶ መን/ግ/ፕ/ት | ||
| 3 | ከሰም የዋና ቦይ ጥገና ፕሮጀክት | 302 | |
| 4 | የወልቂጤ ከተማ መ/ግ/ፕ እና ሰበታ-ቆሬ ከ/መ/ጥ/ፕ | 158 | |
| 5 | (አለምገና-ቡታጅራ-ሆሳና፣ አረካ ከ/መ/ጥ/ፕ፣ | 150 | |
| 6 | [አዳማ -አዋሽ-ሚሌ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት | 127 | 0 |
| 7 | አዲስ-አዳማ-አሰላ መ/ግ/ፕ/ት | 175 | |
| 8 | ዱለቻ- አዋሽ አርባ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት | 250 | 0 |
| 9 | አዋሽ-ሚሌ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት | 383 | 0 |
| 10 | ሞጆ ደረቅ ወደብ ግንባታ ፕሮጀክት | 80 | 0 |
| 11 | ጊዳቦ ግድብና ካናል ግንባታ ፕሮጀክት | 380 | 0 |
| 12 | ዲማ ራድ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት | 700 | 0 |
| 13 | ኮንግ -በጎንዲ-ወንበራ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት | 750 | |
| 14 | አርጆ ዲዴሳ ስኳር ልማት መስኖ ግንባታ ፕሮጀክት | 380 | |
| 15 | ጉደር ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት | 175 | 0 |
| 16 | ርብ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት | 686 | |
| 17 | መገጭ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት | 733 | 0 |
| 18 | ግሸን-መገንጠያ መ/ግ/ፕ/ት | 480 | |
| 19 | ወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት | 1185 | 25 |
| 20 | ኩራዝ ግድብ፣ካናል እና መንገድ ግ/ፕሮጀክቶች | 960 | |
| 21 | ጅንካ መንደር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት | 883 | |
| 22 | የሳላይሽ-ኦሞ መ/ግ/ፕ | ||
| 23 | ያቤሎ ባይ-ፓስ መ/ግ/ፕሮጀክት፣ፕ/ት | 600 | |
| 24 | ሰመራ ዩኒቨርሲቲ መጠጥ ውሃ ግ/ፕ፣ ተንዳሆ እርሻ | 595 | |
| 25 | አክሱም-ሽሬ ከ/ጥ/ፕ | 1041 | |
| 26 | ካዛ ግ/ግ/ፕ | ||
| 27 | ተንዳሆ የዋና ቦይ ጥገና እና የተንዳሆ እርሻ ሥራ | 600 | |
| 28 | ሚሌ-ጋላፊ፡ዲቸቶ መገንጠያ መ/ሥ/ፕ | 680 |
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን